1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የፕራግ ማራቶን ውድድር በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያዉያን አሸነፉ

እሑድ፣ ሚያዝያ 26 2017

በቼክ ሪፑብሊክ ዋና ከተማ ፕራግ ዛሬ የተካሄደውን የወንዶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሚ ብርሃኑ አሸነፈ። ለሚ ለሁለት ተከታታይ አመታት የፕራግ ውድድርን በማሸነፍ እስካሁን በፕራግ በተካሄዱ 30 ውድድሮች ክብረ ወሰኑን ያስጠበቀ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆንም በቅቷል።

Tschechien Prag 2025 | ORLEN Prag Marathon | Äthiopier Lemi Berhanu Hayle gewinnt
ምስል፦ Michal Kamaryt/CTK/IMAGO

በቼክ ሪፑብሊክ ዋና ከተማ ፕራግ ዛሬ የተካሄደውን የወንዶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሚ ብርሃኑ አሸነፈ። ለሚ ለሁለት ተከታታይ አመታት የፕራግ ውድድርን በማሸነፍ እስካሁን በፕራግ በተካሄዱ 30 ውድድሮች ክብረ ወሰኑን ያስጠበቀ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆንም በቅቷል። ለሚ ውድድሩን ለመጨረስ የፈጀበት ጊዜ 2 ሰዓት ከ 5 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ ነው። አትሌቱ ሁለተኛ ከወጣው ኬንያዊ ፊሊክስ ኪፕኮች ገና ከ 30ኛው ኪሎ ሜትር በፊት ተነጥሎ በመውጣት ያለ ማንም ተፎካካሪ ሊያሸንፍ ችሏል። ጃፓንያዊው ቴትሱያ ዮሮኢሳካ ከአራት ደቂቃ ገደማ በኋላ ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል።

የወንዶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሚ ብርሃኑ አሸነፈምስል፦ Michal Kamaryt/CTK/IMAGO

በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ በርቀቱ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች

በሴቶች መካከል የተደረገው ውድድር እስከ ማጠናቀቂያው ድረስ ልብ አንጠልጣይ ሆኖ ቆይቷል። በመጨረሻም ኢትዮጵያዊቷ ብርቱካን ወልዴ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ 55 ሰከንድ በሆነ ሰአት አሸናፊ ሆናለች። ከብርቱካን 30 ሰከንድ ብቻ በመዘግየት ኬንያዊቷ ኢቫሊን ቺርቺር ሁለተኛ በመግባት የማጠናቀቂያ መስመሩን ስታቋርጥ የሀገሯ ልጅ ፓስካልያ ቼፕኮጌ ሶስተኛ ሆናለች።

ኢትዮጵያዊቷ ብርቱካን ወልዴ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ 55 ሰከንድ በሆነ ሰአት አሸናፊ ሆናለችምስል፦ Michal Kamaryt/CTK/IMAGO

ኢትዮጵያውያን ባሸነፉበት የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ቻይና ሮቦቶች ከሰዎች አወዳደረች

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካዋ ማያሚ እያስተናገደች ባለው የግራንድ ስላም የሩጫ ውድድር በ1500 ሜትር ሴቶች ኢትዮጵያዊቷ ፍሬወይኒ ኃይሉ በድንቅ አጨራረስ አሸንፋለች። ፍሬወይኒ ርቀቱን ለመጨረስ 4:06.96 ወስዶባታል። በውድድሩ ብርቱ ፍክክር ያደረገችው አሜሪካዊቷ ኒኪ ሂልስ ሁለተኛ ስትሆን የወሰደባት ጊዜም 4:07.08 ሆኗል። በርቀቱ የጃማይካውን ግራንድ ስላም አሸናፊ የነበረችው ድርቤ ወልተጂ ሶስተኛ ወጥታለች።

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW