የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ጥሪ
ዓርብ፣ ሚያዝያ 15 2013![Äthiopien | Rahel Bafe](https://static.dw.com/image/57317251_800.webp)
ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ወጥቶ መግባት እና በሕይወት የመኖር ዋስትና ፈፅሞ የማይታሰብበት ደረጃ ላይ ደርሳለች ሲል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተናገረ። የአገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ አንድነትን ከሚያናጋ ተግባር እንዲቆጠብ የጠየቀው የጋራ ምክር ቤቱ፣ መንግሥት ለአገር ፀጥታና ሰላም በቁርጠኝነት እንዲሠራ ፣ ለንፁሐን ዜጎች ሞትም ፍትሕ እንዲሰጥ ጠይቋል። ስድስተኛው አጠቃላይ ምርጫ እጅግ ስጋት ያዘለ ቢሆንም ሕዝብ ቅቡልነት ያለው መንግሥት ይፈጥር ከሆነ ምርጫው መደረጉ የግድ ነው ብሏል ምክር ቤቱ።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ
እሸቴ በቀለ