1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ1ኛ ዓመት የዮንቨርሲቲ ተማሪዎች ተሞክሮዋ

ዓርብ፣ ጥቅምት 15 2006

ኢትዮጵያ ውስጥ አጋጣሚዎች ካልፈቀዱ በስተቀር ከቤተሰብ ተለይቶ መኖር ብዙም አልተለመደም። ከነዚህ ከአጋጣሚዎች አንዱ ወጣቶች ለዮንቨርስቲ ትምህርት ወደ ሌላ ከተማ ተመድበው ሲሄዱ ነው።

ምስል DW

ለመሆኑ የመጀመሪያ ዓመት የዮንቨርሲቲ ተማሪዎችን ምን ይጠብቃቸዋል? እንዴትስ ይወጡታል? ለትምህርት ከሚኖሩበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ተመድበው የተጓዙ ሶስት ወጣቶች በመጀመሪያ ዓመት የዮንቨርሲቲ ቆይታቸው ስለጠበቁት እና ስለ አገኙት አጫውተውናል። እዮሲያስ ማሞ ተወልዶ ያደገው በናዝሬት ከተማ ነው። የ18 ዓመቱ የምህንድስና ተማሪ ለትምህርት ወደ ደብረ ታቦር ከሄደ 2ኛ ሳምንቱን ይዟል። ከወላጆቹ ተለይቶ ለረዥም ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ሲሄድ የመጀመሪያ ጊዜው ነው። የሚማርበት ዮንቨርስቲ የመጀመሪያ ምርጫው አልነበረም። ቢሆንም በቦታው ደስተኛ ነው። የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎቹ ትምህርት ከጀመሩ ዛሬ አምስተኛ ቀናቸው ነው።

ሌላዋ ወጣት ቤተልሔም አጥናፉ ትባላለች። ለትምህርት ከድሬደዋ ወደ አዲስ አበባ የመጣችው በመስከረም ወር መጨረሻ ነው። ወጣቷ ትናንት ምዝገባ ማጠናቀቃቸውን ነግራናለች። ትምህርት ገና አልተጀመረም። ምን እያረገች ነው? አጫውታናለች።

ምስል DW

እንደ ቤተልሔም ሁሉ ሀሰን ነገየ የድሬደዋ ልጅ ነው። የተመደበው ግን መቀሌ ከተማ ነው። ሀሰን ትምህርት ስላልተጀመረ ወደ ከተማ እንጂ ወደ ቤተ መፅሀፍት እስካሁን አልሄደም። ከሀገር ጉብኝት ሌላ የትምህርት ዝግጅቱ ምን ይመስላል?

ሁሉም ወጣቶች ከሌሎች ተማሪዎች ጋ ማደሪያ ክፍል መጋራት ግድ ይላቸዋል። አብረው ሲኖሩ ቅርብ ጊዜ ቢሆንም የእስካሁኑ የጋራ ህይወት ምን ይመስላል? በሰፊው ገልፀውልናል።

ተማሪዎች የትም ሀገር ይኖሩ የት ስለ ምግብ ሲጠየቁ ብዙውን ጊዜ የትምህርት ቤት ምግብ አይጣፍጠንም ይላሉ። ወጣቶቹ በምግብ አቅርቦቱ ደስተኛ ይሆኑ? ሌላስ ምን ፈተና ገጥሟቸው ይሆን? ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW