1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአዲሱ ዓመት የኢትዮጵያውያን ተስፋ

ዓርብ፣ ጳጉሜን 3 2015

አንድ ዓመት አልቆ አዲሱ ሲመጣ ሰዎች አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ዕቅድ የሚያስቡ የሚያልሙበት ነው። 2015 ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ፈታኝ ዓመት ነበር። ከሦስት ቀናት በኋላ የሚጀምረው አዲሱ 2016 ዓም ምን ይዞ ይኾን? የብዙዎች ጥያቄና ጉጉት ነው።

ፎቶ፤ የአዲስ ዓመት ድባብ በአዲስ አበባ
ከሦስት ቀናት በኋላ የሚጀምረው አዲሱ 2016 ዓም ምን ይዞ ይኾን? የብዙዎች ጥያቄ ነው። ፎቶ፤ የአዲስ ዓመት ድባብ በአዲስ አበባምስል Seyoum Getu/DW

የሕዝብ አስተያየት

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ ውስጥ ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ ባልተረጋጋው የፖለቲካ ሁኔታ የሰላምመናጋት እና የኑሮ አለመረጋጋት ነዋሪዎችን ሲፈትን፤ በርካቶችንም ሲያስጨንቅ መስተዋሉ የተለመደ ጉዳይ እየሆነ የመጣ መስሏል። በ2010 ዓ.ም. በመሃል የታየው መረጋጋት እና የለውጥ ስሜት እምብዛም ሳይዘልቅ አንዴ በታዋቂ ግለሰቦች ግድያ በሌላ ጊዜ ደግሞ ንጹሐን ላይ በሚፈጸሙ የጅምላ ግድያ እና ግጭቶች የተነሳ ተስፋዎች እየደበዘዙ ውጥረት ስፍራውን ሲይዝ ተስተዋለ። በተለይም ደግሞ ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በትግራይ ክልል የፈነዳው የከፋው የእርስበርስ ጦርነት ለድፍን ሁለት ዓመታት ዘልቆ በ2015 ዓ.ም. መጀመሪያ መቋጫ ቢያገኝም ትላልቆቹ የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች፤ ብሎም በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የግጭትና ግድያ ዜናዎችን መስማት እንደቀጠለ ነው። ኢትዮጵያ አሮጌውን 2015 ዓ.ም. ሸኝታ አዲሱን 2016 ዓ.ም. ለመቀበል ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋታል። ኢትዮጵያውያንም ስለአዲሱ ዓመት መልካሙን ማለም ጀምረዋል፡፡ ለመሆኑ በአዲሱ ዓመት በኢትዮጵያ ምን ይከሰት ይሆን? አዲሱ የኢትዮጵያውያን ዓመት አገሪቱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በከፋ መልኩ እየተፈተነችበት የመጣችውን የግጭት ሰቆቃዎችን የምትገላገልበት ይሆን? የተወሰኑ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጠይቀናል።

የዋጋ ንረት በአንድ በኩል፤ በሌላው የጸጥታ ስጋት ቢያጠላበትም ለአዲስ ዓመት በጎው ተስፋ ማድረግ ብዙዎች መርጠዋል። ፎቶ አዲስ አበባ የበዓል ዋዜማ ድባብምስል Seyoum Getu/DW

ሥዩም ጌቱ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW