1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የ2023 የጅቡቲ የእንደራሴዎች ምክርቤት ምርጫ

ሰኞ፣ የካቲት 20 2015

ጅቡቲ በተለይ በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ እንደምትገባ በማስረጃ የተደገፉ ሪፖርቶች ለፌደራልና ለአፋር ክልል መንግሥት ማቅረባቸውን የገለጹት አቶ ጋዓስ ይሁንና ተድበስብሶ እንዳለፈ ለዶቼ ቬለ /DW/ ተናግሯል።

Schiffe vor der Küste von Dschibuti im Golf von Aden
ምስል፦ MAZEN MAHDI/EPA

የ2023 የጅቡቲ የእንደራሴዎች አባላት ምርጫ

This browser does not support the audio element.

ጅቡቲ በአለፈው ዓርብ የምክር ቤት አባላት ምርጫ አካሂዳለች። በምርጫው ከአንድ በስተቀር የተቃዋሚ ፓርቲዎች እንዳልተሳተፉ ሪፖርቶች ያመላክታሉ። 65 መቀመጫ ላለው ወንበር በተካሄደ ምርጫ ከሰባቱ በስተቀር ገዚው ፓርቲ እንዳሸነፈ እየተነገረ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ሂደቱን በቅርበት የሚከታተሉት የዓፋር ሰብአዊ መብት ድርጅት የበላይ ሐላፊ ከሆኑት አቶ ጋዓስ አሕመድን አነጋግረናቸዋል። እንደ አቶ ጋዓስ ገለጻ ጎረቤት ሃገር ጅቡቲ ከዓመት በፊት ፕረዚደንታዊ ምርጫ ያካሄደች ሲሆን አሁን ዓርብለት የተካሄደው ምርጫ ደግሞ የእንደራሴዎች ምክርቤት ምርጫ ነው።
በዚህ ምርጫ እንደሳቸው አገላለጽ የመንግስት ተለጣፊ ከሆነ አንድ ፓርቲ በስተቀር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከምርጫው እራሳቸውን አግልለዋል።
እስከ አሁን ይፋዊ ያልሆኑ የምርጫ ውጤቶች እንዳመላከቱት ከ65 መቀመጫዎች ከሰባቱ በስተቀር ሁሉንም ወንበሮች ገዢው ፓርቲ ጥርግርግ አድርጎ ``እንዳሸነፈ`` ይገልጻሉ አቶ ገዓስ።
ጅቡቲ በተለይ በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ እንደምትገባ በማስረጃ የተደገፉ ሪፖርቶች ለፌደራልና ለዓፋር ክልል መንግስት ማቅረባቸውን የገለጹት አቶ ጋዓስ ይሁንና ተድበስብሶ እንዳለፈ ለDW ተናግሯል።
የአሁኑ ምርጫ ተቃዋሚዎችና አማራጭ ሐሳብ ያልቀረበበት ነው ያሉት አቶ ጋዓስ የነበረው አገዛዝ ስለሚቀጥል በውጭ ግኑኝነት በኩል የሚሻሻል ነገር እንደማይኖር ተናግረዋል።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW