1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ63 ኩባንያዎች የማዕድን ማምረትና ምርምር ፈቃድ ተሰረዘ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 6 2013

በማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በማዕደን ማምረትና ምርምር ላይ እንዲሰማሩ ፈቃድ ከተሰጣቸው ተቋማት ውስጥ የ63ቱ ፈቃድ መሰረዙን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዐስታወቀ፡፡ ፈቃድ የተሰረዘባቸው ተቋማት በተገቢው ወቅት የተሰጣቸውን ፈቃድ ባለማሳደሳቸው፤ ከአቅም በታች በማምረትና የሚጠበቅባቸውን ክፍያ ያልፈጸሙ ናቸው ተብሏል።

Äthiopien | Regierungsministerium | Takele Uma
ምስል Seyoum Hailu/DW

ባለፉት 5 ወራት ከማዕድን ዘርፍ 302.9 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገልጧል

This browser does not support the audio element.

በማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በማዕደን ማምረትና ምርምር ላይ እንዲሰማሩ ፈቃድ ከተሰጣቸው ተቋማት ውስጥ የ63ቱ ፈቃድ መሰረዙን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዐስታወቀ። የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ታከለ ዑማ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት፦ ፈቃድ የተሰረዘባቸው ተቋማት በተገቢው ወቅት የተሰጣቸውን ፈቃድ ባለማሳደሳቸው፤ ከአቅም በታች በማምረትና የሚጠበቅባቸውን ክፍያ ያልፈጸሙ ናቸው። ሚኒስትሩ በመግለጫው እንዳሉት በሜድሮክ ኢትዮጵያ በሻኪሶ-ለገደምቢ ሲተገበር የነበረው የማዕድን ማውጣት ተግባር ችግሮቹ ተቀርፎ ወደ ሥራ ይመለሳል። በሌላ በኩል ባለፉት ሁለት ወራት በትግራይ ክልል ሲመረት የቆየው በወር 346 ኪ.ግ. የሚገመት፤ ባጠቃላይም ከ700 ኪ.ግ. በላይ ወርቅ ወደ ማዕከላዊው ብሔራዊ ባንክ ሳይገባ ቀርቷል ተብሏል፡፡ ባለፉት አምስት ወራት ከማዕድን ዘርፍ 302.9 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱም ታውቋል።
ሥዩም ጌቱ 
ማንተጋፍቶት ስለሺ
እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW