ዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያው ጦርነት በፍጥነት መቋጫ እንዲያገኝ ትሻለች
ረቡዕ፣ ጥር 4 2014ማስታወቂያ
ዩናይትድስቴትስ በኢትዮጵያ የሚካሄደው ጦርነት መቋጫ በሚያገኝበት መንገድ ላይ ትኩረት ሰጥታ በመሥራት ላይ መሆኗን አስታወቀች። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ ኔድ ኘራይስ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ጦርነት ወደ ፍፃሜ ለማምጣት አሜሪካ ጠንካራ ዲኘሎማሲ እየተከተለች ነው። በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ያለው ቀውስ ለዩናይትድስቴትስ ፈታኝ ሆኖ መቆየቱን አንድ የአሜሪካ አስተዳደር ከፍተኛ ባለሥልጣን መናገራቸው ተመልክቷል።
ታሪኩ ኃይሉ
ታምራት ዲንሳ
ማንተጋፍቶት ስለሺ