1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዩክሬይን እና የዩሊያ ቲሞሼንክ ዕጣ ፈንታ

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 18 2004

የቀድሞ የዩክሬይን ጠቅላይ ሚንስትር ዩሊያ ቲሞሼንኮ እአአ በ 2004 ዓም በዩክሬይን የተካሄደው ብርቱካናማ ዓብዮት በመባል የሚታወቀው የሕዝብ ዓመፅ ታዋቂ መሪ ነበሩ። አሁን ግን በሥልጣን ዘመናቸው ፈፅመዉታል በተባለዉ ሙስና ሰባት አመት እስራት ተፈርዶባቸው ባለፈው ነሀሴ ወር 2011ዓም ወህኒ የወረዱ ሲሆን፡

ARCHIV - Die ehemalige ukrainische Regierungschefin Julia Timoschenko sitzt in einem Gerichtssaal in Kiew, Ukraine, am 04 Juli 2011. Die kranke, ukrainische Ex-Regierungschefin Julia Timoschenko hat angeblich eine Behandlung in einer Klinik verweigert und ist zurück ins Straflager gebracht worden. «Es war unmöglich, sie im Krankenhaus zu behalten. Das ist kein Hotel», sagte die stellvertretende Gesundheitsministerin der Ex-Sowjetrepublik am Sonntag (22.04.2012) nach Medienangaben. (Zu dpa "Timoschenko zurück aus der Klinik ins Straflager") EPA/SERGEY DOLZHENKO pixel
ምስል picture-alliance/dpa

የእሥር ሁኔታቸውን በመቃወም ካለፉት ጥቂት ቀናት ወዲህ የረሀብ አድማ መተዋል። ይህና ካባድ የጤና እክል ያጋጠማቸው ቲሞሼንኮ ወደ ሐኪም ቤት ሲወሰዱ ሳለ በወህኒ ቤቱ ጠባቂዎቻቸው ተደብድበዋል በሚል የተሰማውም ዜና እንዳሳሰባቸው የአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን እና ሩስያ ገልጸዋል።

በሰሜን ምሥራቅ ዩክሬይን በሚገኘው የቻሪኪቭ ወህኒ የረሀብ አድማ ከመቱ ዛሬ አምስተኛ ቀን የሆናቸው ቲሞሼንኮ እአአ በ 2005 እና ከ 2007 እስከ 2010 ዓም ድረስ ጠቅላይ ሚንስትር በነበሩበት ጊዜ ከሩስያ ጋዝ እንዲገዛ በተፈራረሙት ውል ሰበብ ነው ለእሥር የበቁት። በዛሬው ዕለት በአንጻራቸው አዲስ ችሎት የሚከፈትባቸው ቲሞሼንኮ ባደረባቸው ከባድ የጀርባ ሕመም ምክንያት ባለፈው የሣምንት መጨረሻ ሐኪም ቤት በተወሰዱበት ጊዜ የመደብደብ ምልክት እንደታየባቸው ጠበቃቸው ሴርጌይ ቭላሴንኮ አረጋግጠዋል።
« ዩሊያ ቲሞሼንኮ ባለፈው ዓርብ በወህኒ ቤቱ ጠባቂዎች ተደብድበዋል። በሆዳቸዉና እጆቻቸዉ ላይ ደም የቋጠሩ ቁስሎች ታይተዋል። ቲሞሼንኮ ካለፈቃዳቸው በግድ ሰው ተሸክሞ መኪና ውስጥ አስገብቶ ወደ ሐኪም ቤት ወስዷቸዋል። ባለፈው እሁድ ደግሞ ወደ ወህኒ ቤት መልሰዋቸዋል። »
ቲሞሼንኮ በመታመማቸው ወደ ሐኪም ቤት መወሰዳቸውን ቢያረጋግጥም፡ ተደብድበዋል መባሉን ሀሰት ሲሉ አስተባብለዋል፤ ሐኪም ቤት ከደረሱ በኋላ ሕክምና እንዲደረግላቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸውም ወደ ወህኒ ቤት እንዲመለሱ መደረጉን ዓቃቤው ሕግ አክለው ገልጸዋል።
ካሁን ቀደም ከቤርሊን በሄዱ ጀርመናውያን ዶክተሮች ሕክምና ተደርጎላቸው የነበሩት ቲሞሼንኮ  ወደሌላ አውሮጳዊ ሀገር ሄደው እንዲታከሙ ለማስቻል ዩክሬይን ሕጉን ለማሻሻል ዝግጁ መሆንዋን የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ቫለሪ ኮሮሽኮቭስኪ ገልፀዋል። በምላሹ የአውሮጳ ህብረት ከዩክሬይን ጋ በእንጥልጥል ያለውን የፖለቲካ እና የንግድ ውልን እንዲያጸድቅ ጠይቀዋል። ይሁንና፡ ህብረቱ የቲሞሼንኮ ጉዳይ እልባት ሳያገኝ፡ አንዳንዶች አውሮጳውያን ባለሥልጣናት እንደሚሉትም፡ የቀድሞዋ ጠቅላይ ሚንስትር ሳይፈቱ ውሉን እንደማያጸድቅ አስታውቋል።
የጀርመን ፕሬዚደንት ዮአኺም ጋውክ በዩክሬይን ላይ ያለውን የምዕራቡን ዓለም ቅሬታ ለማሳየት ሲሉ በሚቀጥለው ግንቦት ወር በዩክሬይን ሊያደርጉት የነበረውን ጉብኝት ሰርዘዋል። የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጊዶ ቬስተርቬለ የፍትሑ አውታር ለፖለቲካው ንትርክ መሣሪያ መሆን እንደማይገባው አሳስበዋል።
« ዩክሬይን ከአውሮጳ ህብረት ጋ በይበልጥ ለመቀራረብ ከፈለገች የሕግ የበላይነትን የመሳሰሉትን መሠረታዊ አውሮጳውያን እሴቶች ማክበር አንዱ ቅድመ ግዴታ ነው። በዚሁ ቅድመ ግዴታ ውስጥ የወንጀለኛ መቅጫው ሕግ ለፖለቲካው ውዝግብ መሣሪያ መሆን የለበትም የሚለው ሀሳብ ይገኝበታል። »
የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ትናንት ባወጣው መግለጫም፡ የዩሊያ ቲሞሼንኮ መብት እንዲከበር ከመጠየቁ ጎን፡ የሀገሪቱን ውስጣዊ ችግሮች ሳያባብሱ ለተፈጠረው ውዝግብ መፍትሔ እንዲፈለግለት ጠይቆዋል።
ዩክሬይን እና ፖላንድ እአአ ከሰኔ ስምንት እስከ ሀምሌ አንድ ቀን ድረስ የአውሮጳ እግር ኳስ ዋንጫ ግጥሚያን ሊያስተናግዱ ስድስት ሣምንታት በቀረው ባሁኑ ጊዜ በምዕራቡና በዩክሬይን መካከል በቲሞሼንኮ ሰበብ ውዝግቡ እየተጠናከረ መጥቶዋል። ባለፈው ሣምንት በማጭበርበርና ግብር ባለመክፈል ሌላ አዲስ ክስ የተመሠረተባቸው ቲሞሼንኮ እና ምዕራቡ ዓለም ክሱን ፕሬዚደንት ያኑኮቪች ተቀናቃኛቸውን ለመጉዳት እንዳደረጉት ነው የተመለከቱት።
 ጠበቃቸው ሴርጌይ ቭላሴንኮ የችሎቱን ሂደት ተዓማኒነት የሌለው ሲሉ ወቅሰዋል።
« ለዩሊያ ቲሞሼንኮ የሚሟገተው ቡድን፡ ልክ እንደ ዘጠና ዘጠኝ ከመቶው የሀገሪቱ ሕዝብ በዩክሬይን የፍትሕ አውታር ላይ እምነት የለውም። በዚህም የተነሳ ከዩክሬይን ውጭ ያሉ ፍርድ ቤቶችን ከለላ እናፈላልጋለን። »
ጠበቃው ቭላሴንኮ በዚሁ አነጋገራቸው የቲሞሼንኮን ጉዳይ የቀድሞዋ የዩክሬይን ጠቅላይ ሚንስትር ተገቢው ሕክምና እንዲደረግላቸው ባለፈው ወር ጥያቄ ላሳሰበው የአውሮጳ የሰብዓዊ መብት ፍርድ ቤት ለማቅረብ ዕቅድ እንዳላቸው ጠቁመዋል። በዩክሬይን ትልቁ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድን በቲሞሼንኮ ላይ ተፈፀመ የተባለው በደል እንዲጣራ ጠይቋል።

ፕሬዚደንት ያኑኮቪችምስል AP
ምስል picture-alliance/dpa

ማርኩስ ዛምባሌ/አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW