ይሁንታ ያገኘዉ አዲስ ህገመንግስት በኬንያ
ሐሙስ፣ ሐምሌ 29 2002ማስታወቂያ
ድምፁን ለመስጠት ከተመዘገበዉ ከ12ሚሊዮን በላይ ከሆነዉ መራጭ መካከል እንካሁን ከተቆጠረዉ 73በመቶዉ ይሁንታዉን ለአዲሱ ህገመንግስት ሰጥቷል። እንዲያም ሆኖ ህገመንግስቱ ተቀባይነት አግኝቶ ጸደቀ ማለት ወዲያዉ ተግባራዊ ይሆናል ማለት አይደለም። ኬንያ ግን በአመፅና በግጭት ታጅቦ እስከዛሬ ከሚጠቀሰዉ ያለፈዉ ወቅት ምርጫ ተሸጋግራ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የፈለገዉን ድምፅ ሰጥቶ የገባባት አገር ለመሆን በቅታለች።
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ