1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዲፕሎማቶችና የዉጭ ሃገር ዜጎች ሱዳንን እየለቀቁ መሆኑ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 16 2015

በሱዳን ጦር ሰራዊትና የፈጥኖ ደራሽ ኃይል መካከል የሚካሄደው ጦርነት ሱዳንን ወደለየለት ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ ከቷታል። በሁለቱ ኃይሎች መክከል ሲደረጉ ከቆዩት የሰባዊ የተኩስ ማቆም ስምምነቶች አንዱም የተከበረ ባለመሆኑ በተለይ ካለፈው ዓርብ ወዲህ የምዕራባውያን፣አረብ መንግስታትና ለሎች ዜጎቻቸውን ለማስወጣት ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል።

Deutschland | Luftwaffe evakuiert Bundesbürger aus dem Sudan
ምስል፦ Jörg Carstensen/dpa/picture alliance

በሱዳን የነበሩ ጀርመናዉያን ዛሬ መዲና በርሊን ደርሰዋል

This browser does not support the audio element.

አስረኛ ቀኑን የየያዘው በሱዳን ጦር ሰራዊትና  የፈጥኖ ደራሽ ኃይል መካከል የሚካሄደው ጦርነት፤ ሱዳንን ወደለየለት ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ ከቷታል።  በሁለቱ ኃይሎች መክከል ሲደረጉ ከቆዩት የሰባዊ የተኩስ ማቆም ስምምነቶች አንዱም የተክበረ ባለመሆኑ በተለይ ካለፈው ዓርብ ወዲህ የምዕራባውያን፣አረብ መንግስታትና ለሎችም አገሮች  ዜጎቻቸውን ከሱዳን ባስቸኳይ ለማስወጣት ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሜሪካ፤ ጀርመን፤ ፈርንሳይ፤ እስፔንና ሌሎችም መንግስታት በየግላቸውና በጋራ ባደርጓቸው ስምሪቶች በርካታ ዜጎቻቸውን በተለይም ዲፕሎማቶቻቸውን ከካርቱም ለማስወጣት ችለዋል። 

ምዕራባዉያን ሃገራት ከሱዳን የማዉጣቱ ሂደት ምስል፦ État-major des armées

የህብረቱ የውጭ ጉዳይ ሀልፊ ሚስተር  ጆሴፍ ቦርየል ዛሬ እረፋድ ላይ በሉክዘምበርግ  በሰጡት አስተያየት 21 የህብረቱን ድፕሎማቶችንና ሰራተኖችን ጨምሮ በርክታ የህብረቱ ዜጎች ከሱዳን ሊወጡ መቻላቸውን አረጋግጠዋል። “ የሳምንቱ መጨረሻ ዜጎቻችንን ከሱዳን ለማስወጣት ጥረት ስናደርግ የቆየንባቸው ረጅም ቀናት ነበሩ።  21 የህብረቱ ሰራተኖች አውርፓ ደርሰዋል፤ ከአንድ ሺ በላይ የህብረቱን ዜጎች ደግሞ ከሱዳን ማስወጣት ተችሏል በማለት  ዜጎችን ለማስወጣት በተደረገው ጥረት የተካፈሉትን ሁሉና በተለይም የፈረንሳይን መንግስት አምስግንዋል። ሚስተር ቦይርየል የህብረቱ አምባሳደር ግን በዚያው በሱዳን ከካርቱም ውጭ ሁኔትዎችን እየተከታተሉ እንደሚቆዩም አስታውቀዋል።

አሜሪካም ኤም ኤች-47 የተሰኙ ሂሊኮብተቿን ወደ ሱዳን አስገብታ አንድ መቶ የሚሆኑ ዲፕሎማቶቿንና ቤተስቦቻቸውን ከካርቱም ማስወጥቷ ተገልጿል። ጀርመንና ፈረንሳይም በርካታ የየራሳቸውንና የሌሎች አገሮችን ዲፕሎማቶች በተደጋጋሚ በረራዎች ማሰወጣታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ የብርታኒያ የመከላከያ ሚኒስተር ቤን ዋላስ በበኩላቸው፤ “ ባለፈው ምሺት የብርታኒያ ሰራዊት ወደ ካርቱም ስምሪት በማድረግ ዲፕሎማቶቹን በተሳከ ሁኔታ ከካርቱም አስወጥቷል በማለት ስምሪቱም የአየርና ባህር ሀይሎችን ያሳተፈ እንድነበር አስታውቀዋል።

ምዕራባዉያን ሃገራት ከሱዳን የማዉጣቱ ሂደትምስል፦ État-major des armées

ሳኡዲ አረቢያም በፖርት ሱዳን በኩል በመርከብ የበርካታ አገሮች ዲፖሎማቶንችና ዜጎችን ማስወጣቷ ታውቋል። ግብጽ በበኩሏ ከአስር ሺበላይ ዚጎቿ በሱዳን እንደሚኖሩ ገልጻ የቻሉት ፖርት ሱዳን ወደ ሚገኘው የግብጽ ቆንስላ እንዲሄዱ አሳስባለች። ሌሎች አገሮች፤ ቻይናና ሩሲያን ጨምሮ ሁሉም፤ ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማሰውጣት የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ እንደሆነም ታውቃኡል።

ይህች ዛሬ ሁሉም ሊለቃት የሚጣደፍባት አገር ሱዳን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ከጎረቤት አገሮች የመጡ ስደተኖች የሚኖሩባት ወይም ወደ ሊላ ሶስተኛ አገር የሚተላለፉባት እንደሆነች የሚታወቅ ሲሆን፤ ዛሬ፤  ሁሉም አገሮች ዋና ትኩረታቸውና ጥድፊያቸው  ዜጎቻቸውን እንደምንም ብለው ከሱዳን ማውጣት እንጂ ለሱዳን ችግር አለመሆኑ አስዛኝ መሆኑን ብዙዎች ይጠቅሳሉ።

ሱዳን ወደዚህ ችግር ወስጥ የገባችው በዋናነነት በአገሪቱ ውስጥ ሁለት ተገዳዳሪና የኢኮኖሚ አቅም ጭምር ያላቸው የሰራዊት ክፍሎች በመኖራችውና አዛዦቻቸውም የፖለትካ ስልጣን ፍላጎት  ያላቸው በመሆኑ ነው የሚሉት ታዛቢዎች፤ ሁለቱም የጦር አዛዦች የሚደግፏቸው የውጭ ሀይሎች ያሏቸው መሆኑ  ደግሞ፤ የሱዳንን ፖለቲካ የበለጠ ውስብስብ እንደሚያደርገውና ጦርነቱንና  ፖቲካዊ ቀውሱንም ሊያራዝመው እንደሚችል ያላቸውን ስጋት  ይገልጻሉ።

 

ገበያው ንጉሴ

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW