1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዳግም የኤች አይቪ ተሐዋሲ ስርጭት ስጋት

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 4 2009

በዓለም አቀፍ ደረጃ የHIV ተሐዋሲን ስርጭት እስከ በጎርጎሪዮሳዊዉ 2030ዓ,ም ለመቀነስ እና ብሎም የኤድስ በሽታን ስጋትነን ለማብቃት ታቅዷል። የUNAIDS መረጃ እንደሚያሳየዉ በዚሁ የዘመን ቀመር 2015 መጨረሻ ድረስ በተሐዋሲዉ 36,7 ሚሊየን ሰዎች ተይዘዋል። እስካለፈዉ ሰኔ ወር ደግሞ 18,2 ሚሊየን ሰዎች የፀረ HIV መድኃኒት አግኝተዋል።

Symbolbild AIDS HIV Afrika Jugendliche
ምስል Getty Images/AFP/T. Kitamura

ዳግም የኤች አይቪ ተሐዋሲ ስርጭት ስጋት

This browser does not support the audio element.

UNAIDS እንደሚለዉ ከጎርጎሪዮሳዊዉ 2010ዓ,ም ወዲህ አዲስ በተሐዋሲዉ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ብዙም ሲቀንስ አልታየም። በየዓመቱም 1,9 ሚሊየን ገደማ ሰዎች አዲስ በኤች አይቪ መያዛቸዉን ያመለክታል። በሌላ በኩል ላለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ የኤች አይቪ ተሐዋሲ ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ፤ አዲስ በበሽታዉ የሚያዙ ሰዎችም ቁጥርም እንዲሁ እየቀነሰ መምጣቱ በተደጋጋሚ ሲነገር ቆይቷል። በቅርቡ ደግሞ በተሐዋሲዉ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሄዱ ተነግሯል። የበሽታዉን ስርጭት ለመከላከል ይደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች መቀዛቀዛቸዉን የሚያመላክቱ አሉ። ሙሉ ቅንብሩን ከድምጽ ዘገባዉ ያድምጡ፤

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW