1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ድሬደዋ: የጭነት መኪና አሽበርካሪዎች ቅሬታ

ቅዳሜ፣ ታኅሣሥ 10 2013

ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ጭነት ይዘው ድሬደዋ ጉሙሩክ የደረሱ ከአንድ መቶ በላይ ተሽከርካሪዎች ጭነቱ ሳይራገፍ ከ17 ቀናት በላይ በመቆም ለእንግልት ተዳርገናል ሲሉ አሽከርካሪዎቹ ቅሬታ አቀረቡ፡፡ የድሬደዋ ጉሙሩክ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በበኩሉ መኪኖቹ የቆሙት በእኔ ምክንያት አይደለም ይላል።

Äthiopien LKW-Fahrer Protest in Dire Dawa
ምስል፦ M.Teklu/DW

This browser does not support the audio element.

ለDW ቅሬታ ያቀረቡ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ከጅቡቲ ይዘውት የመጡት ጭነት ሳይረገፍ ለረዥም ቀናት በመቆየታቸው ለእንግልት እና ላልተገባ ወጪ መዳረጋቸውን ተናግረዋል ፡፡
የንብረቱ አስመጪ የሆነው ድርጅት መንግስት በፈቀደው የቀረጥ ነፃ ፍቃድ ዕቃውን ማምጣቱንና አሁን የተፈጠረው መስተጓጎል በጉሙሩክ በኩል በአሰራር የተፈጠረ እንደሆነ አስረድቷል፡፡ በመጉለላቱም ንብረቱ እየተጎዳ ይገኛል ብሏል፡፡
የደሬዳዋ ጉሙሩክ መቅረጫ ጣቢያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ስራ አስኪጅ አቶ ደመላሽ በጉዳዩ ላይ ለ DW በሰጡት ምላሽ ችግሩ የተፈጠረው ቅርንጫፉ በሚሰጠው አገልግሎት አሰጣጥ አይደለም ፤ ቀረጥ ነፃን በሚመለከት በፌደራል ደረጃ የወጣውን መመርያ መሰረት አድርጎ ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡
የጉሙሩክ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ አስመጭዎቹ እንዲከፍሉ የተጠየቁትን ታክስ እንዲከፍሉ ወይም የገንዘቡን መጠን ተቀማጭ ገንዘብ (ዲፖሲት) አስይዘው እቃውን እንዲያራግፉ እና ቅሬታ እንዲያቀርቡ አማራጭ ሰጥቻለሁ ብሏል፡፡ ይኸው ተፈፃሚ ካልሆነ ዕቃውን ማራገፍ አስቸጋሪ መሆኑንም ተናግሯል፡፡

መሳይ ተክሉ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW