1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ድርቅ፣ ረሃብና የአገር በቀል አዝርእት፣

ረቡዕ፣ ሐምሌ 20 2003

የመንግሥታት መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ የገንዘብና የግብርና ተቋማት ፤ የመንግሥት ያልሆኑ የግብረ-ሠናይ ድርጅቶችና በሰብአዊ እርዳታ ላይ ያተኮሩ ታዋቂ ዓለም አቀፍ የኪነ ጥበብ ሰዎች፤

ምስል AP

በድርቅ ሳቢያ በመራብ ላይ ላለው የምሥራቃዊው አፍሪቃም ሆነ የአፍሪቃው ቀንድ ህዝብ፤ ለጊዜው፤ አያሌ ሜትሪክ ቶን እህልና የበሰለ ምግብ እንዲቀርብለት በመማጸን ላይ ናቸው።

ድርቅን ለመቋቋም ፤ ረሃብንም ለመታገል፣ ለዘለቄታው፤ የአገር አቀፍ የሰብል አዝርእትንና ዕጽዋትን ጠቀሜታም ሆነ ድርሻን፤ አያያዝንም በተመለከተ ሳይንቲስቶች ምን ይላሉ? ሳይንስና ኅብረተሰብ ዝግጅታችንን ይከታተሉ---

በአሁኑ ወቅት፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው የመወያያ አርእስት ከሆኑት ጥቂት ዐበይት ጉዳዮች አንዱ፤ ከ 60 ዓመታት ወዲህ ምሥራቃዊውን አፍሪቃ፣ ኢትዮጵያን ጭምር እጅግ ክፉኛ እንደመታ የሚነገርለት ድርቅና ረሃብ ነው። በድርቁ ሳቢያ ፤ ለረሃብ የተጋለጠው 12 ሚሊዮን ያህል ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንዲደረግለት ተማጽኖ እየቀረበ ነው። በሰሜናዊው ኬንያ ፤ ቀቢፀ-ተስፋ ያደረባቸው አርብቶ አደሮች፤ ከብቶቻቸው በውሃና በእሳር እጦት እየተሰቃዩ ከሚሞቱ ቢገላገሉ ይሻላል በማለት መግደል መጀመራቸው እየተነገረ ነው። ረሃብንና ድርቅን ለመቋቋም ፣መላው፣ ምን ይሆን? የሥነ-ፍጥረት ጠበብት ምን ይላሉ? በአገር-በቀል የእህል ዘር ፤ ሰፊ ምርምር በማድረግና እንዲጠበቅም ባደረጉት አስተዋጽዖ የታወቁት ፣ Right Livelihood Award የሚሰኘው የአማራጩ የኖቤል ሽልማት ባለቤት ፣ ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት--ዶ/ር መላኩ ወረደ---

(ድምፅ) «ዋናው ጉዳይ-----------------------ማጎልበት!»

ተገን ወይም አለኝታ ያሏቸው ፣ አገር በቀል አዝርእት፣ እንዲሁም ዕጽዋት ያላቸው ጠቀሜታ በቀላሉ የሚታይ አይሆንም። በመሆኑም እነርሱ የሚስፋፉበትንና የሚጠበቁበትን

ሁኔታ ማጎልበት የግድ የሚል መሆኑን ዶ/ር መላኩ ይናገራሉ፣ ይመክራሉ። ማጎልበት ሲባል በትክክል ምን ማለት ይሆን?---

(ድምጽ)----ማጎልበት ሲባል--እርምጃ መውሰድ ነው።»

ጤፍ ፤ማሽላ ፤ ስንዴ፤ ገብስ፤ ባቄላ፤ አተር፣ ሌሎች ሌሎችም የኢትዮጵያ አገር በቀል አዝርእት ምርታማናታቸው እንዴት ነው ሊጨምር የሚችለው? የምርቱ መጠን ከፍ እንዲል ለማድረግ ምን ዓይነት ሳይንሳዊ እርምጃ መውሰድ ይቻላል?

(ድምጽ)«-------------------------»

አገር በቀል አዝርእትና ዕጽዋት እንዲስፋፉና እንዲጠበቁ ከመንግሥትና ከተለያዩ የመንግሥትም ካልሆኑ የግብርና ድርጅቶች ያገኘው ድጋፍ እስከምን ድረስ ነው ይላሉ? የቱን ያህል ትኩረት ተሰጥቶታል?

ተክሌ የኋላ

ሒሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW