1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ድርቅ ያስተጓጎለው የመማር ማስተማር ሂደት በሶማሌ ክልል

ዓርብ፣ መጋቢት 9 2014

በሶማሌ ክልል ድርቅ ከአንድ ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደት እንዲቋረጥ ማስገደዱ ተገልጸ።  በክልሉ ድርቅ ጉዳት ባስከተለባቸው አካባቢዎች ለሚኖረው ማኅበረሰብ የምግብ ፣ የውሀ እና ሌሎች ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑንም የክልሉ መንግሥት አስታውቋል።

Somalia | Dürre
ምስል Messay Teklu/DW

የድርቅ ተጽዕኖ በሶማሌ ክልል

This browser does not support the audio element.

በሶማሌ ክልል የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ የተዘጉ ትምህርት ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር የሚያስችል ተግባር እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ። ድርቁ በክልሉ ከአንድ ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደት እንዲቋረጥ አስገድዷል።  በሶማሌ ክልል ድርቅ ጉዳት ባስከተለባቸው አካባቢዎች ለሚኖረው ማኅበረሰብ የምግብ ፣ የውሀ እና ሌሎች ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑንም የክልሉ መንግሥት አስታውቋል። በዚህ መሀልም በክልሉ የተለያዩ ዞኖችን ለችግር ለዳረገው ድርቅ በቅርቡ የሚጠበቀው የበልግ ዝናብ መፍትሄ ያመጣል በሚል ተስፋ ተደርጓል።

መሳይ ተክሉ 

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW