ጀርመን ሽቱትጋርት ውስጥ ደማቁ ድባብ ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት
ዓርብ፣ ሰኔ 28 2016![Deutschland | Fußball Europameisterschaft 2024 |](https://static.dw.com/image/69574506_800.webp)
ማስታወቂያ
ጀርመን ሽቱትጋርት ውስጥ ደማቁ ድባብ ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት
ለፍፃሜ የተጠበቁት በሩብ ፍፃሜ ሊፋለሙ ነው
በጥንታዊቱና ታሪካዊቱ ሽቱትጋርት ከተማ ጀርመን እና ስፔን ከጥቂት ሰአታት በኋላ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ለመግባት ይፋለማሉ ። የጀርመን እና የስፔን ብሔራዊ የእግር ኳስ ደጋፊዎች ከወዲሁ የተሟሟቁ ይመስላል ። በተለይ የጀርመን ደጋፊዎች በኮይኒግ ሽትራሰ ተሰባስበው እጅግ በደመቀ ሁኔታ ድጋፋቸውን ከወዲሁ እየገለጡ ነው ። «ወደ ቤርሊን እንጓዛለን» ሲሉም በተደጋጋሚ በጀርመንኛ ሲዘምሩ ተደምጠዋል።
የ2016 ዓ.ም የአውሮፓ ዋንጫ መክፈቻ እና የጀርመን ድል
ቤርሊን የዋንጫ ጨዋታ የሚደረግባት ከተማ ናት ። ዛሬ ሽቱትጋርት አሬና ውስጥ ከምሽቱ አንድ ሰአት በሚጀምረው የሩብ ፍፃሜ ግጥሚያ ለመታደም ደጋፊዎች ወደ ከተማዪቱ እየተመመሙ ነው ።
ብዙዎች በዛሬው ግጥሚያ በምድብ ማጣሪያው አንድም ግብ ያልተቆጠረበት የስፔን ቡድን ያሸንፋል ሲሉ ገምተዋል ። የጀርመን ቡድን የዛሬውን የሩብ ፍፃሜ ካሸነፈ ዋንጫው ቤርሊን ውስጥ ይቀራል ሲሉም አክለዋል ።
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ታምራት ዲንሳ
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር