ጅዳ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ት/ቤት
ሐሙስ፣ ጥር 28 2001ማስታወቂያ
በትምህርት ቤቱ ህንፃ ላይ በደረሰዉ የመሰረት መሸሽና የመሰንጠቅ ችግር የመማር ማስተማር ሂደቱ ተቋርጦ ሰንብቶ ከ22 ቀናት በኋላ ተመልሶ መጀመሩን የሳዉዲዉ ወኪላችን ዘገባ ያመለክታል። አዲሱ ትምህርት ቤት አብዛኛዉ ኗሪ ከሚኖርበት ከከተማዉ ወጣ ያለ ቢሆንም በትምህርት ሂደቱ መስተጓጎል የተቸገሩ ወላጆች ተቀብለዉታል። ሆኖም ለዘላቂ መፍትሄዉ ወላጅ ኮሚቴን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቆንስላ የማኅበረሰቡን አባላት ሁሉ አሰባስቦ መላ ካልፈለገለት ለ6ወራት የተያዘዉ የአዲሱ ትምህርት ቤት ዉል ሲያበቃ የመማር ማስተማርሂደቱ ዳግም ችግር ሊገጥመዉ እንደሚችል ስጋታቸዉን እየገለፁ ነዉ።