1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ

እሑድ፣ ሚያዝያ 6 2011

ከባሻገር ባሻገር፤ እንቅልፍ እና ሴት፤ እየሄዱ መጠበቅ፤ እንዲሁም ከሴተኛ አዳሪ የተኮረጀ ሳቅ የተሰኙ የግጥም እና ወግ መድብሎችን በተከታታይ ባለፉት ዓመታት አሳትሟል። አፍቄሜሌፅ በሚል ርዕስም የተዘጀ የግጥም ሲዲ ለስነጽሑፍ ቤተሰቦች አቅርቧል።

CD Belay Bekele Woya
ምስል Belay Bekele Woya

«የግጥም ታዳሚያን መበራከታቸውን ዕድል ይለዋል»

This browser does not support the audio element.

ስለትምህርት ስናወራ እየተማረ ሞተ ብባል ይሻለኛል እና በዚህ ምክንያት ዛሬም ተማሪነኝ ነው ያለኝ። ስነግጥምን የሚገልፅበት ቃል እንደሌለው የሚናገረው ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ ለሀገሩ ለኢትዮጵያ ያለው ፍቅር ደግሞ ከምንም እንደሚበልጥበት አጫውቶኛል። 

ምስል Belay Bekele Woya

ግጥሞችን መጻፍ ከጀመረ ስድስት ሰባት ዓመታት እንደሆኑት የሚናገረው በላይ በቀለ ወያ፤ ሙሉ ጊዜውን ለኪነጥበብ እና ስነጽሑፍ ሰጥቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በወር አንድ ቀን ማክሰኞ የግጥም ምሽት ከባልደረባው ጋር በመሆን ያዘጋጃል። ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ የግጥም ምሽቶች እየተበራከቱ ታዳሚዉም ቁጥሩ እየጨመረ መሄዱንም አስተውሏል። ጎህ በተሰኘው የግጥም ምሽቱ እስከ አንድ ሺህ ሰዎች ይታደማሉ። የእሱን እና የባልደረቦቹን የጥበብ ሥራዎች በአካል ለማድመጥም ወር በገባ በሁለተኛው ሳምንት ማክሰኞ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ብቅ ያለ መንፈሱን አርክቶ እንደሚመለስ ነው ከቆይታችን የተገነዘብኩት።

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW