1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጉልበት ሰጭ መድኃኒትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ

Merga Yonas Bulaማክሰኞ፣ የካቲት 22 2008

ጉልበት ሰጪ መድኃኒት በመጠቀም በተጠረጠሩ ዘጠኝ ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ላይ ምርመራ እንደተጀመረ የኢትዮጵያ የፀረ ጉልበት ሰጪ መድኃኒት መሥሪያ ቤት አስታወቀ። ከዘጠኙ አምስቱ ታዋቂ ሯጮች ናቸው።

Symbolbild Doping
ምስል picture-alliance/dpa/G. Breloer

[No title]

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ የፀረ ጉልበት ሰጪ መድኃኒት መሥሪያ ቤት ዋና ጸሐፊ አቶ ሰሎሞን መዓዛ እንዳስታወቁት፣ ጉልበት ሰጪ መድሀኒት ተጠቅማችኋል በመባል የተጠረጠሩት አትሌቶችን ምርመራ የሚያካሂደው የዓለም አትሌትክስ ፌዴሬሸን ማህበር ነው። አቶ ሰለሞን ግን የአትሌቶቹ ማንነትም ሆነ ወሰዱት የተባለው የመድሀኒት ዓይነት ምንነትን ከመናገር ተቆጥበዋል። ምርመራውን እያካሄደ ያለዉ የዓለም አትሌትክስ ፌዴሬሸን ማህበር ከኢትዮጵያ የአትሌትክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በመሥራት ላይ ይገኛል።

የአዲስ አበባ የስፖርት ጋዝጤኛዉ ምስጋናዉ ለዶይቸ ቬሌ እንደተናገረው፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሸን ዛሬ ጥዋት ይፋዊ ያልሆነ ስብሰባ አካሂዶ ታዋቂ አትሌቶች ይህን ጉዳይ አስመልክተው ለሌሎች ልምዳቸዉን እንዲያካፍሉ ጠይቆዋል። ጉዳዩ በአብዛኛዉ ህዝብ ዘንድ ድንጋጤ መፍጠሩን ምስጋናዉ ገልጾዋል።

ምስል Haimanot Tiruneh


የምርመራው ውጤት እስኪታወቅ ድረስ ህብረተሰቡ መደምደሚያ ሀሳብ ላይ ከመድረስ እንዲቆጠብ ያሳሰበው ታዋቂዉ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ጉዳዩ አሉታዊ የሆነ ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ለዶይቼ ቬለ ተናግሮዋል።

በዙህ ጉዳይ ላይ በዶቼ ቬለ የፌስቡክ ድረ ገፅ ላይ የተወያዩ ተሳታፊዎች ይህ ቅሌት እዉን ከሆነ ትልቅ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር እና ተጠያቂ የሚደረገውም የአትሌቲክሰ ፌዴሬሸኑን መሆኑን አስታውቀዋል።

መርጋ ዮናስ

አርያም አብራሃ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW