የጋዜጠኛ ጌታቸዉ ሽፈራዉ ብይንና በኤሬቻ አደጋ ሁለት ሰዎች መከሰሳቸዉ
ዓርብ፣ ግንቦት 18 2009ማስታወቂያ
ክሱን የመብት ተሟጋቾች ፕረስ ነፃነት ላይ የተሰነዘረ ጥቃት ብለዉታል። እንደ አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዘገባ ከሆነም፤ ካለፈዉ ዓመት ታኅሳስ ወር ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኘዉ ጋዜጠኛ ጌታቸዉ፤ ከተያዘበት አንስቶ ጊዜዉ ሲሰላ በቅርቡ ሊፈታ ይችላል። ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በዋለ ሌላ ችሎት በኢሬቻ በዓል ላይ ለተፈጠረዉ ትርምስ ምክንያት ናቸዉ የተባሉ ሁለት ሰዎች በአሸባሪነት ክስ እንደተመሰረተባቸዉ ታዉቋል። ይህን ክስ አስመልክቶ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ፤ ክሱ ለኛ አዲስ ነዉ የምናጠናዉ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። ሙሉዉን ዝርዝር ዘገባ የድምፅ ማድመጫ ማዕቀፉን በመቻን ያድምጡ።
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ