1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ኤኮኖሚሰሜን አሜሪካ

ግሪንላንድ በዳቮሱ ጉባኤ፣ ዩናይትድ ስቴትስና የአውሮጳ ኅብረት መሪዎች ፍጥጫ

ገበያው ንጉሤ
ዓርብ፣ ጥር 15 2018

ስዊትዘርላንድ ዳቮስ ውስጥ የዓለም የኤኮኖሚ መድረክ የተከናወነበት ይህ ሳምንት አውሮጳውያንን በጥፍራቸው ያስቆመ ነበር ። በተለይ ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በግሪንላንድ ላይ የያዙት አቋም ለአውሮጳውያን ብርቱ ራስ ምታት ሁኖ ዘልቋል ።

የአውሮጳ ኅብረት አስቸኳይ ጉባኤ
የአውሮጳ ኅብረት አስቸኳይ ጉባኤ በብራስልስምስል፦ EU/Xinhua/picture alliance

የትራምፕ፥ አውሮጳ ፍጥጫ

This browser does not support the audio element.

ስዊትዘርላንድ ዳቮስ ውስጥ የዓለም የኤኮኖሚ መድረክ የተከናወነበት ይህ ሳምንት አውሮጳውያንን በጥፍራቸው ያስቆመ ነበር ። በተለይ ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በግሪንላንድ ላይ የያዙት አቋም ለአውሮጳውያን ብርቱ ራስ ምታት ሁኖ ዘልቋል ። ዋነኛ የውጥረቱ ሰበብ የዴንማርክ ግዛት የሆነችው እና ከሩስያ ትይዩ በአርክቲክ ንፍቀ ክበብ ውስጥ ውቅያኖሱ ላይ የተንሳፈፈችው ግሪንላንድ ናት ።

ዶናልድ ትራምፕ «መሬትም እኮ አይደለችም አንዳች ግዙፍ ቁራጭ በረዶ» ሲሉ የገለጧት ራስ ገዟ ግሪንላንድ ። የአሜሪካው ፕሬዚደንት፦ በዚህም አለ በዚያ ጠቅልዬ ወደ ግዛቴ አካትታለሁ ሲሉ መዛታቸው ውጥረቱን አጉልቶት ቆይቷል ። አውሮጳውያኑ አስቸኳይ ጉባኤ እንዲይዙም አስገድዷቸዋል ።

ስለ ሰሞነኛው እሰጥ አገባ እና ስለ አውሮጳውያኑ አስቸኳይ ጉባኤ እንዲነግረን የብራስልስ ወኪላችን ገበያው ንጉሤን ስቱዲዮ ከመግባታችን በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።

የዳቮስ የዓለም ኤኮኖሚ መድረክ ባለፈው ሰኞ በይፋ ጀምሮ የተጠናቀቀው ዛሬ ነው የዴንማርክ ግዛት ስለሆነችው ራስ ገዟ ግሪንላንድ በዳቮስ መድረክ የነበረው አወዛጋቢ ውይይት በምን ተቋጨ? ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕስ «የሰላም ቦርድ» ያነሱት ሐሳብ ምንድን ነው የሚለውን ጥያቄ በማብራራት ይጀምራል ።

ሙሉ ቃለ መጠይቁን በድምፅ ከታች በማገናኛው ማድመጥ ይቻላል ። 

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ገበያው ንጉሤ

እሸቴ በቀለ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW