1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ግብጽ እና ህዝባዊ አመፅ

ዓርብ፣ ጥር 20 2003

ዛሬም በቀጥለው የግብፅ ህዝባዊ አመፅ በፖሊስና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት ተፈጠረ።

ምስል AP

ህዝቡን ለማገድ በብዛት የተሰማራው የግብፅ ወታደር ካይሮ እና አሌክሳንድሪያ ከተሞች አደባባይ የወጡ ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጢስና በፕላስቲክ ጥይቶች ለመበተን ሞክሯል ። ፖሊስ ከአርብ የፀሎት ስርዓት ፣ በኃላ በህዝባዊ ሰልፍ ላይ ሊገኙ የተዘጋጁትን የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሀመድ ኤል ባራዳይንም ወደ ሰልፉ እንዳያቀኑ ከልክሏል ። በዛሬው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ የሀገሪቱ ዋነኛ ተቃዋሚ ንቅናቄ «የሙስሊም ወንድማማቾች » ተካልፍለዋል ። ኤል ባራዳይ ለዚሁ ዓላማ ግብፅ መዲና ካይሮ በገቡበት በትናንትናው ዕለት እንደተናገሩት ወደ ሀገራቸው የሄዱት ሁሉም ነገር በሰላማዊ መንገድ መከናወኑን ለማረጋገጥና ሰለማዊ የተቃውሞ ሰልፎችን ለመሩት እና ላደራጁት ወጣቶች የፖለቲካ ፣ የመንፈስ እና የሞራል ድጋፍ ለመስጠት ነው ። አዲሲቷን ግብፅ ማየት እሻለሁ ያሉት ኤልባራዳይ በእስከዛሬዎቹ የትግል ስልቶች ውጤት ሊገኝ አለመቻሉንም ገልፀዋል ።

ግብፅ ውስጥ ከትናንት ምሽት አንስቶ በአጠቃላይ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎት ማለትም የኢንተርኔት እና የሞባይል ስልክ እንዲሁም የ SMS አገልግሎቶች ተቋርጠዋል ። ቁጥራቸው 20 የሚደርስ የሙስሊም ወንድማማቾች ንቅናቄ አባላት ትናንት ለሊት ከየቤታቸው ተወስደው ታስረዋል ። ከመካከላቸው 5 የቀድሞ የህዝብ ዕንደራሴዎች ይገኙበታል ። የቱኒዝያውን የጀስሚን አብዮት ተከትሎ በካይሮ ከሱዌዝ በአሌክሳንደሪያ እና በሌሎችም ከተሞች በተቀሰቀሰው የግብፁ ህዝባዊ አመፅ ሂዩመን ራይትስ ዎች እንደሚለው እስካሁን 8 ሰላማዊ ሰልፈኞችና አንድ ፖሊስ ተገድለዋል ። የግብፅ ህዝባዊ አመፅ በተቀጣጠለበት በዚህ ወቅት ላይ አሜሪካን አመፅ ለችግሩ መፍትሄ አይሆንም አይደለም ስትል አስጠንቅቃለች ። በሌላም በኩል የአሜሪካን ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ትናንት ባስተላለፉት መልዕክት የግብፁ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክ የፖለቲካ ተሀድሶዎችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል ። መንግስት ም ሆነ ህዝቡ የየበኩላቸውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል ።

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW