1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ግብፃዊቷን የገደለዉ ተፈረደበት

ረቡዕ፣ ኅዳር 2 2002

ድሬዝደን ያስቻለዉ ፍርድ ቤት-ገዳዩን አሌክሳንደር ቪየንስ ለግድያዉ ሙሉ በሙሉ ጥፈተኛ አድርጎታል።

ገዳዩ ፍርድ ቤትምስል AP

ምሥራቅ ጀርመን ዉስጥ ባለፈዉ ሰኔ ማብቂያ አንዲት ግብፃዊት ነብሰ ጡር ወይዘሮን ፍርድ ቤት አዳራሽ ዉስጥ በጩቤ ጨቅጭቆ የገደለዉ ጀርመናዊ ወጣት ዛሬ እድሜ ልክ እስራት ተበየነበት።የሃያ-ስምንት አመቱ ወጣት ግብፃዊቱን ወይዘሮ በገደለበት ወቅት ባለቤቷንም አቁስሎ ነበር። ግድያዉና የጀርመን መንግሥት ፈጥኖ ግድያዉን አለማዉገዙ ከፍተኛ ቁጣና ተቃዉሞ አስከትሎ ነዉ የሰነበተዉ።ዛሬ ድሬዝደን ያስቻለዉ ፍርድ ቤት-ገዳዩን አሌክሳንደር ቪየንስ ለግድያዉ ሙሉ በሙሉ ጥፈተኛ አድርጎታል።ፍርዱ ከመሰጡት በፊት ሥለ ሒደቱ የበርሊን ወኪላችን ይልማ ሐይለ-ሚካኤልን በስልክ አነጋግሬዉ ነበር።

ነጋሽ መሐመድ/ይልማ ሐይለ ሚካኤል
አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW