“ግጭትና መፍትሄው
ሐሙስ፣ ጥቅምት 29 2005ማስታወቂያ
ይህ “እንዳባቶቻችን” የተሰኘው ተከታታይ የሬዲዮ ድራማ ክፍል ሰባት ዝግጅታችን ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት ዝግጅታችን ከዕርቀ-ሠላሙ በኋላ በኪጃኒ ሸለቆ ህይወት ምን ያህል ሠላማዊ እንደሆነች ተመልክተናል፡፡ ግን ኬሮና ሶምባ ቶሩቤዎችን በኪምቤቤዎች ላይ ለማስታጠቅ ፕሬዚዳንት ማቶንጌን ለማሳመን ከመሞከራቸው አንፃር ያ ሠላም ምን ያህል ዘላቂ ይሆን? አስታውሱ ዋነኛ ዓላማቸው በምርጫው ዓመት ግጭት መቀስቀስ ነው፡፡ ያ ማለት በጦርነት በምትታመሰው የኪጃኒ ሸለቆ ያኔ ምርጫ አይኖርም ማለት ነው፡፡ እስኪ የዛሬውን ጭውውት ምን ሊከሰት እንደሚችል አብረን እንከታተል፡፡ በኪጃኒ ሸለቆ ውስጥ ማለዳ ላይ ነው፡፡ ኒናና ባለቤቷ ማሳምቦ እጎጆው ደጃፍ ላሞቹን እያለቡ ነው፡፡
ኬሪስፒን ማኪዴዎ
አዜብ ታደሰ