1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ግጭት ጦርነት ያጠላበት ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ

እሑድ፣ ሰኔ 2 2016

ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የሃይማኖት ሰዎችና ዜጎች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በሚታሰሩበት፤ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል ከመንግሥት ኃይሎች የታጠቁ ኃይሎች በይፋ በሚዋጉበት በዚህ ወቅት እንዴት ያለ ሀገራዊ ምክክር ነው የሚካሄደው በማለትም ይሞግታሉ።

 ሀገራዊ ምክክር ባለፈው ሳምንት መጀመሩ ይፋ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ለሐገራዊ ምክክሩ ማስተዋዋቂያ ካሰራጫቸዉ መልዕክቶች አንዱምስል Seyoum Getu/DW

ግጭት ጦርነት ያጠላበት ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ

This browser does not support the audio element.

ለረዥም ጊዜያት በተስፋ የተጠበቀው ሀገራዊ ምክክር ባለፈው ሳምንት መጀመሩ ይፋ ሆኗል። በመንግሥት ከተሰየመ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን «ኢትዮጵያ እየመከረች ነው» በሚል መሪ ቃል አዲስ አበባ ላይ ለሰባት ቀናት ያካሄደው መድረክ የመወያያ አጀንዳዎችን ለመለየት የመጀመሪያው ምዕራፍ ነው ብሏል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የሄደው ችግር መነሻው ፖለቲካዊ ነው የሚሉ ወገኖች ምንም እንኳን ሀገራዊ ምክክር መታሰቡን ቢደግፉም ሂደቱ ላይ ጥያቄዎችን በማንሳት አንዳንዶቹ እራሳቸውን ማግለላቸውን በይፋ እያሳወቁ ነው።

ከኮሚሽኑ አመሰራረት አንስቶ የገዢው ፓርቲ ጣልቃገብነትን አጥብቀው የሚተቹትም መድረኩ አካታችነት ይጎድለዋል በሚል ከወዲሁ አዎንታዊ ውጤት እንደማይጠብቁ ይገልጻሉ።

ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የሃይማኖት ሰዎችና ዜጎች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በሚታሰሩበት፤ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል ከመንግሥት ኃይሎች የታጠቁ ኃይሎች በይፋ በሚዋጉበት በዚህ ወቅት እንዴት ያለ ሀገራዊ ምክክር ነው የሚካሄደው በማለትም ይሞግታሉ። ግጭት ጦርነት ያጠላበት ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ የዚህ ሳምንት የዶቼ ቬለ የእንወያይ ርዕሰ ጉዳይ ነው። 

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW