“ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሥልጣን ይልቀቁ” የኦሮሞ ተቃውሞ አራማጆች
ዓርብ፣ ሰኔ 26 2012ማስታወቂያ
ድምፃዊ ሐጫሉ ሁንዴሳ ተገድሎ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ 35 ሰዎች ከታሰሩ በኋላ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የተቃውሞ ዘመቻ በመካሔድ ላይ ይገኛል። ፌስቡክ እና ትዊተርን በመሳሰሉ ማኅበራዊ ድረ ገፆች በሚካሔደው ዘመቻ ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል የድምፃዊ ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ፣ ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፋጣኝ ሥልጣን እንዲለቁ፣ የዘፈቀደ ግድያዎች ይቁሙ የሚሉት ይገኙበታል።
ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፤ በሚቀጥሉት አምስት ወራት ነጻ እና ፍትኃዊ ምርጫ እንዲካሔድ፤ የተቋረጠ የኢንተርኔት እና የመደበኛ ስልክ አገልግሎት ወደ ሥራ እንዲመለስ የሚሉ ጥያቄዎችም ቀርበዋል።
እነዚህ ጉዳዮች መልስ ካልተሰጣቸው በጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ላይ ዓለም አቀፍ ማዕቀብ እንዲጣልም ግፊት ያደርጋል። እሸቴ በቀለ ተቃውሞውን የሚያስተባብሩትን ዶክተር ሔኖክ ገቢሳን በስልክ አነጋግሯቸዋል።
እሸቴ በቀለ
ኂሩት መለሰ