1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና 

እሑድ፣ መስከረም 11 2012

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና በነበራቸው ቆይታ የኮሎኔል በዛብሕ ጴጥሮስ ጉዳይ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች ስምምነት አንድ አካል እንደሆነ መናገራቸውን በውይይቱ የተሳተፉት የሐዲያ ዞን አስተዳደር የፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን አባይነሕ ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል። 

Äthiopien | Premier Minister Abiy Ahmed besucht Hosaena
ምስል Ethiopian Prime Minister Office

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና 

This browser does not support the audio element.

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ወደ ሖሳዕና አቅንተው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸው ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል በዞኑ ነዋሪዎች የሚነሳው የክልል አደረጃጀት ጉዳይ፤ የሥራ አጥነት እና የወጣቶች ፍልሰት እና የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ እጣ-ፈንታን የተመለከቱ ጉዳዮች ይገኙበታል። 
ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ጦርነት ወቅት የሚያበሩት ተዋጊ የጦር አውሮፕላን ተመቶ ከወደቀ በኋላ በኤርትራ እጅ የገቡት ከ21 አመታት ገደማ በፊት ነበር። ኮሎኔሉ እስካሁን በሕይወት ስለመኖራቸው ግልፅ ያለ ማረጋገጫ ከኤርትራም ይሁን ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ወገን አልተገኘም። 

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሖሳዕና በነበራቸው ቆይታ የኮሎኔል በዛብሕ ጴጥሮስ ጉዳይ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች ስምምነት አንድ አካል እንደሆነ መናገራቸውን በውይይቱ የተሳተፉት የሐዲያ ዞን አስተዳደር የፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን አባይነሕ ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል።  


ሸዋንግዛው ወጋየሁ
እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW