1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ጦርነት ያወደማቸው የጤና ተቋማት ተስፋ 

እሑድ፣ ታኅሣሥ 24 2014

ከአንድ ዓመት በላይ በዘለቀው በሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረገው ጦርነት በመሰረተ ልማት ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ውድመት እያደረሰ ቀጥሏል። እስካሁን በትግራይ ክልል ስለደረሰው የጉዳት መጠን በትክክል የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ጦርነቱ በተዛመተባቸው የአፋር እና አማራ ክልሎች ከ2000 በላይ የጤና ተቋማት ተዘርፈዋል፤ አልያም ከአገልግሎት ውጭም ሆነዋል።

Äthiopien | Tigray Konflikt | Zerstörung durch militante Tigray Gruppen
ምስል፦ Alemenew Mekonnen/DW

እንወያይ፦ጦርነት ያወደማቸው የጤና ተቋማት ተስፋ 

This browser does not support the audio element.

ጦርነት ያወደማቸው የጤና ተቋማት ተስፋ 

ከአንድ ዓመት በላይ በዘለቀው በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚደረገው ጦርነት በመሰረተ ልማት ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ውድመት እያደረሰ ቀጥሏል። እስካሁን በትግራይ ክልል ስለደረሰው የጉዳት መጠን በትክክል የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ጦርነቱ በተዛመተባቸው የአፋር እና አማራ ክልሎች መንግሥት እንደገለጸው ከ2000 በላይ የጤና ተቋማት ተዘርፈዋል፤ ወድመዋል፤ ከአገልግሎት ውጭም ሆነዋል። እንደኢትዮጵያ ባለ የጤና ዘርፉ የተዳከመ ሀገር የደረሰው ጉዳት በተገልጋዩ ኅብረተሰብ ላይ የሚያስከትለው ጫና ቀላል እንዳልሆነ ይታመናል። ስለደረሰው ጉዳት እየተወራ ዛሬም ጦርነቱ አለማባራቱ ቀጣይ ሊከተል የሚችለውን ውድመት አሳሳቢ ያደርገዋል። በአማራ እና አፋር ክልል የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ የማቋቋም እንቅስቃሴ መጀመሩ አንድ ነገር ቢሆንም ከውጭ ምንዛሪ እጥረቱ ጋር ተያይዞ የመድኃኒት እና የህክምና መገልገያዎች አቅርቦትም ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው። የደረሰውን ጉዳት በማንሳት፣ ካለው ላይ የተቀነሱትን የጤና ተቋማት ዳግም ለአካባቢው ማኅበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ የማድረግ ጥረት እና ያለውን አቅም በሚመለከት የተካሄደውን ውይይት የድምጽ ማዕቀፉን በመጫን ያድምጡ። 

ምስል፦ Maria Gerth-Niculescu/DW
ምስል፦ Maria Gerth-Niculescu/DW
ምስል፦ Alemenew Mekonnen/DW

ሸዋዬ ለገሠ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW