1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፈረንሳይ፣ ተቃዉሞ እና አድማ

ሐሙስ፣ ኅዳር 27 2011

በሕዝባዊዉ ተቃዉሞ አድማ ምክንያት የቀድሞ አቋሙን የለወጠዉ የፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮ መንግስት በነዳጅ ዘይት ዋጋ ላይ የተደረገዉን የዋጋ ጭማሪ ለስድስት ወር በሥራ ላይ እንዳይወል አግዷል

Frankreich Gelbwesten-Protest in Paris
ምስል Getty Images/AFP/G. van der Hassel

አድማዉ የሐገሪቱን ምጣኔ ሐብት እያሽመደመደዉ ነዉ

This browser does not support the audio element.

የፈረንሳይ መንግስት በነዳጅ ዘይት ላይ ያደረገዉን የዋጋ ጭማሪ በመቃወም በተለያዩ  ከተሞች የተደረገ እና የሚደረገዉ የአደባባይ ሰልፍ እና አድማ የሐገሪቱን ምጣኔ ሐብት እያሽመደመደዉ ነዉ።«ቢጫ ሰደርያ » የሚባሉት አድመኞች ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር በገጠሙት ግጭት የሰዉ ሕይወት ጠፍቷል፤ ሐብት ንብረትም ወድሟል። በሕዝባዊዉ ተቃዉሞ አድማ ምክንያት የቀድሞ አቋሙን የለወጠዉ የፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮ መንግስት በነዳጅ ዘይት ዋጋ ላይ የተደረገዉን የዋጋ ጭማሪ ለስድስት ወር በሥራ ላይ እንዳይወል አግዷል። የተቃዉሞ ሰልፉ አስተባባሪዎች ግን ተጨማሪ ተቃዉሞ እንዲደረግ እየጠሩ ነዉ።አንዳድ ፖለቲከኞች ደግሞ መንግስት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲደነግግ እየገፋፉ ነዉ።

ኃይማኖት ጥሩነሕ 

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW