1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ፓሪስ ላይ የተካሄደዉ የጀርመን ፈረንሳይ ትብብር ጉባኤ

ሃይማኖት ጥሩነህ
ዓርብ፣ ኅዳር 12 2018

ባለፉት ዓመታት በቀጠለዉ የሩሲያ ዩክሬይን ጦርነት፤ የኃይልና ቴክኖሎጂ ጥገኝነት በትራንስ አትላንቲክ ትስስር ጥንካሬ እየላላ መምጣትና አስተማማኝ አለመሆን፤ ብሎም የፖለቲካ አለመረጋጋት፤ የአዉሮጳ ዋንኛ አንቀሳቃሽ ሞተር ለሆኑት ለፈረንሳይ ጀርመን ትብብር፤ ጫና ዉስጥ ሊከተዉ መቻሉ ተነግሯል።

ፓሪስ
ፓሪስ ምስል፦ Michel Euler/AP/dpa/picture alliance

ፓሪስ ላይ የተካሄደዉ የጀርመን ፈረንሳይ ትብብር ጉባኤ

This browser does not support the audio element.

ፓሪስ ላይ የተካሄደዉ የጀርመን ፈረንሳይ ትብብር ጉባኤ

ባለፉት ዓመታት በቀጠለዉ የሩሲያ ዩክሬይን ጦርነት፤ የኃይል እና ቴክኖሎጂ ጥገኝነት በአዉሮጳና አሜሪካ ማለትም የትራንስ አትላንቲክ ትስስር ጥንካሬ እየላላ መምጣት እና አስተማማኝ አለመሆን ፤ ብሎም የፖለቲካ አለመረጋጋት፤ የአዉሮጳ ዋንኛ አንቀሳቃሽ ሞተር ለሆኑት ለፈረንሳይ ጀርመን ትብብር ፤ ጫና ዉስጥ ሊከተዉ መቻሉ ተነግሯል። ይህን የፈረንሳይ ጀርመን ትብብርን ለማጠናከር ደግሞ፤ ከመቼዉን ጊዜ በላይ አስፈላጊ እና አፋጣኝ እርምጃ መወሰድ እንዳለበትም እየተነገረ ይገኛል።   አዉሮጳ በኢኮኖሚ በኢንዱስትሪ በቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን በወታደራዊ እና ደህንነት ጊዳዮች ረገድ፤ ልዑዋላዊነትዋን በአስቸኳይ ማጠናከር አስፈላጊ የሆነበት ደረጃ ላይ መድረስዋን የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተቋም በፓሪስ  ላይ በአዘጋጀዉ የሁለቱ ሃገራት ትብብር ወቅታዊ ጉዳዮችን በዳሰሰዉ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ በባለሞያዎቹ አፅኖት ተሰጥቶበታል። ወቅቱም አዉሮጳ በወታደራዊ እና ደህንነት ጉዳዮች እንዲሁም በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ሃገሮች ትስስር «በኔቶ» የወደፊት እጣ ፈንታ ላይም ከዩናይትድ ስቴትስ ጥገኝነት ዉጭ ቆም ብላ፤ ማሰብ የምትጀምርበት ምዕራፍ ላይ መድረስዋም ተመላክቷል።   

ሃይማኖት ጥሩነህ

አዜብ ታደሰ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW