1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የተዋጣው ገንዘብ የት ገባ?

ዓርብ፣ ጥር 16 2017

ሌላው ዐቢይ ችግር ተብሎ የሚጠቀሰው ደግሞ፦ በጦርነቱ ወቅት የተዋጣው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላርና ዩሮ የት ገባ? የሚል ነው። ይህ ጥያቄ በተለያዩ መድረኮች ቢነሳም ጠብ የሚል ምላሽ እንዳልተገኘ ያነጋገርናቸው የማሕበረሰቡ አባላት በምሬት ይገልጻሉ።

ፕሮፌሰር መድሃኔ አስመላሽ
ፕሮፌሰር መድሃኔ አስመላሽምስል፦ privat

አንድ ለአንድ፤ ከፕሮፌሰር መድሃኔ አስመላሽ ጋር

This browser does not support the audio element.

የትግራይ ዳያስፖራ ማሕበራት የገለልተኝነት ጥያቄ
በአውሮፓና ሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ማሕበራት በርካታ አወንታዊ ተግባራት መፈጸማቸው ቢነገርላቸውም የዚያኑ ያህል በበርካታ ጉዳዮች ይወቀሳሉ። አንዱ የሚወቀሱበት ነጥብ ከፖለቲካ ወገንተኝነት አልጸዱም የሚል ነው። በተለያዩ ጊዜያት የሚያዘጋጇቸው መድረኮችም የክልሉ ገዢ ፖርቲ ህወሓትን ለማስደሰት ሲባል የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ያገላሉ በሚል ይተቻሉ ።የትግራይ የተቃዋሚ ፓርቲዎችበውጭ አገራት የሚሳተፉባቸው መድረኮች እንዳይሳኩ እንቅፋቶች መፍጠርና የመሳሰሉት ችግሮችም እንደሚስተዋልባቸው ይነገራል።
ሌላው ዐቢይ ችግር ተብሎ የሚጠቀሰው ደግሞ፦ በጦርነቱ ወቅት የተዋጣው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላርና ዩሮ የት ገባ? የሚል ነው። ይህ ጥያቄ በተለያዩ መድረኮች ቢነሳም ጠብ የሚል ምላሽ እንዳልተገኘ ያነጋገርናቸው የማሕበረሰቡ አባላት በምሬት ይገልጻሉ። በጀርመን ሙኒክ ከተማ የሚኖሩና የትግራይ ማሕበረሰብ በሚመለከቱ ጉዳዮች ንቁ የፖለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉት ፕሮፌሰር መድሃኔ አስመላሽን በነዚህ ጉዳዮች እንግዳ አድርገናቸዋል። መሉ ቃለ ምልልሱን ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኑ።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW