1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

1443ኛው የኢድ አል አድሀ አረፋ በዓል በድሬደዋ ፣ ሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞች

ቅዳሜ፣ ሐምሌ 2 2014

1443ኛው የኢድ አል አድሀ አረፋ በዓል በድሬደዋ ፣ ሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞች በድምቀት ተከብሯል። በዓሉን በመረዳዳት እና በመደጋገፍ እንደሚያከብሩም በየከተሞቹ የሚኖሩ የእምነቱ ተከታዮች ተናግረዋል።

Äthiopien Eid al-Adha
ምስል፦ Messay Teklu/DW

የኢድ አል አድሃ በዓል አከባበር በምስራቅ ኢትዮጵያ

This browser does not support the audio element.

1443ኛው የኢድ አል አድሀ አረፋ በዓል በድሬደዋ ፣ ሀረር እና ጅግጅጋ ከተሞች በድምቀት ተከብሯል። በዓሉን በመረዳዳት እና በመደጋገፍ እንደሚያከብሩም በየከተሞቹ የሚኖሩ የእምነቱ ተከታዮች ተናግረዋል።

በድሬደዋ የሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች "ኢድ ሜዳ" ተብሎ በሚጠራው የበዓሉ ማክበርያ ስፍራ  ከንጋት ጀምሮ በመሰባሰብ በሶላት ስግደት በዓሉን አክብረዋል። ለዶይቼ ቬሌ አስተያየት የሰጡት አቶ ፈርሀን አብዱላሂ ከስግደት መልስ በዓሉን ያለኝን በማካፈል እንደሚያከብሩ ገልፀዋል።

ምስል፦ Messay Teklu/DW

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በበዓሉ በተለይ ወጣቶች ድሬደዋ የምትታወቅበትን የፍቅር እሴት እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። የድሬደዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው "ሙስሊሙ ህብረተሰብ በተለይ ወጣቶች የሽብርተኞችን እና ፀረ ሰላም ኃይሎችን አፍራሽ ሴራ" እንዲያጋልጥ ጥሪ አቅርበዋል።

ምስል፦ Messay Teklu/DW

በዓሉ በጥንታዊቷ ሀረር ከተማም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሯል።የሀረር ነዋሪው አቶ ፈርሀን በበዓሉ መረዳዳት እና ጥላቻን ማስወገድ ይገባል ብለዋል። 1443ኛው የአረፋ በዓል በጅግጅጋም በድምቀት መከበሩን  ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው አቶ ሀሰን የተባሉ ነዋሪ ተናግረዋል።

መሳይ ተክሉ

ታምራት ዲንሳ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW