1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

78ኛው የኢትዮጵያ የድል በዓል

እሑድ፣ ሚያዝያ 27 2011

የኢትዮጵያ አርበኞች ከአምስት ዓመታት ዉጊያ በኋላ የኢጣሊያ ወራሪ ጦርን ድል ያደረጉበት 78ኛ ዓመት በዓል ዛሬ በመላዉ ኢትዮጵያ ተከብሮ ዋለ።

Afrika Veteran Patriots Day in Addis Abeba | Lij Daniel Jote Mesfin & Sahle-Work Zewde, Präsidentin
ምስል፦ DW/G.T. Weldegiorgis

78ኛው የኢትዮጵያ የድል በዓል

This browser does not support the audio element.


የኢትዮጵያ የጥንት አርበኞች ወራሪዉን የኢጣሊያ ጦር ድል ያደረጉበት 78ኛ ዓመት ዕለት ዛሬ ተከበረ። በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው የድል ሀውልት ዙሪያ በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔርና የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር የበላይ ጠባቂ ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፤ የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሕበር ፕሬዝደንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፣ አርበኞችና ቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል። የአድዋ ድልን ጨምሮ አዲስ የመታሠቢያ አደባባይ እንደሚታነፅም በስነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል። 

ወይዘሮ ሳሕለ ወርቅ ለእድምተኛዉ ባደረጉት ንግግር ዕለቱን፣ በኢትዮጵያዉን መካከል ልዩነት ቢኖርም በሐገር ጉዳይ ልዩነት እንደሌላቸዉ ያስመሰከሩበት ነዉ ብለዉታል።በበዓሉ ላይ የተካፈሉ ጥንታዊ አርበኞች በበኩላቸዉ የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ለሐገሩ ነፃነትና ክብር የነሱን አርዓያ እንዲከተል አደራ ብለዋል።ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ቅኝ ለመግዛት ከወረረችበት ከ 1928 ጀምሮ ድል ሆና እስከተባረረችበት እስከ 1933 ድረስ ኢትዮጵያዉያን አርበኞች ለነፃነታቸዉና ለክብራቸዉ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉበትን ዉጊያና ትግል አድርገዋል። 
 

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

 ነጋሽ መሐመድ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW