1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ የፊልም ፌስቲቫል ኦጋዱጉ

ረቡዕ፣ የካቲት 22 2009

አፍሪቃዉያን የፊልም አዘጋጆች ሥራቸዉን ለዉድድር የሚያቀርቡበት በቡርኪናፋሶ ዋና ከተማ ዋጋዱጉ ላይ የሚካሄደዉ የፊልም ፌስቲቫል ዛሬ አምስተኛ ቀኑን ይዟል። ለ10 ቀናት በሚዘልቀዉ በምሕጻሩ ፌስፓኮ በመባል በሚታወቀዉ በዚህ የፊልም ፌስቲቫል ላይ ለአንድ መቶ ሺህ ተመልካቾች ከ100 የሚበልጡ ፊልሞች ለዕይታ እንደሚቀርቡ ተገልጿል።

Afrika-Filmabend: Gerreta und Rumeurs du Lac
ምስል Sileshi Siyoumnor / Neon Rouge

Q&A Manti FESPACO - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

 በዚህ የፊልም ሥራዎች ዉድድር ላይ ለመጨረሻዉ ምርጫ ከቀረቡት 20 ፊልሞች መካከልበአጭር ፊልሞች ዘርፍ የሚሳተፈዉ ባልደረባችን ማንተጋፍቶት ስለሺ ሥራ ግርታ  የተሰኘዉ ፊልምም ተካቷል። ከእሱ ሌላም ፍሬ የተሰኘ ረዥም ፊልሙን ይዞ የቀረበዉ ክንፈ ማሞ በዚሁ ዉድድር በመሳተፍ ላይ ይገኛል። እስካሁን የደረሱበትን ዉጤት ለመገመት ቢከብዳቸዉም ፊልሞቻቸዉ በታዩባቸዉ የተለያዩ አዳራሾች ከተመልካች አበረታች ምላሽ ማግኘታቸዉን ሁለቱም ኢትዮጵያዉያን የፊልም አዘጋጆች ገልጸዉልናል። ስቱዲዮ ከመግባቴ በፊት ወደ ኦጋዱጉ ደዉዩ በአጭሩ አነጋግሬያቸዋለሁ። በቅድሚያ ያገኘሁት ባልደረባዬ ማንተጋቶትን ነዉ።

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW